Pages

Saturday, September 8, 2012

የ2004 ሒሳብ ሲዘጋ

From አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ


እንዳለፉት ጊዜያት ሁሉ በዚህ ዓመትም ሰዎች ከፌስቡክ ውጪ እንዴት እንደሚኖሩ ለማወቅ ጉግል ውስጥ ፈልጌም፣ አስፈልጌም መልስ ማግኘት አልቻልኩም፡፡ ስለዚህ በፌስቡክ ውስጥ መኖሬን ቀጥያለሁ፡፡ በርግጥ ፌስቡክ ምንም አልጎደለበትም፤ እንኳን የሆነው የታሰበው ሳይቀር ይወራበታል፡፡ ለአብነትም የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትርን ሞት መጥቀስ ይቻላል፡፡

ፌስቡክ ምድር ላይ ካለው ‹እቤት-እመስሪያቤት› ምልልስ የተሻለ ፋይዳ ያለው ሥራ ለመስራት የተመቸ ዕድልም ይፈጥራል፡፡ የዳቦ ጉዳይ (bread winning) ሁላችንንም በየሙያችን ቢያሰማራንም፣ የምንናፍቀው እና የሚናፍቀን ሌላ ነገር የለም ማለት መቼም አይደለም፡፡ ኢትዮጵያውያን እርስ በእርስ የምንዋደደውን ያክል የምንወደውና የሚወደንን ዓይነት መንግስት ያገኘንበት ጊዜ እምብዛም ነው፡፡ ይህንን መናፈቅ እና መማከር ደንብ ሆኖ፣ በሌላም፣ ዓመቱን ሙሉ በጻፍናቸው ነገሮች ያስደሰትነው ሰው እንዳለ ሁሉ ያስቀየምነው የለም ማለት ዘበት ነውና፣ ያው የግል ጥቅም ይዞን አለመሆኑ ታውቆ በአዲስ ዓመት ዋዜማ ይቅር መባባልን የመሰለ ነገር የለም፡፡

በዚህ ዓመት በፌስቡክ ገጼ ላይ ያሰፈርኳቸውን እና ከወዳጆቼ ጋር ቅኔ የተዛረፍኩባቸውን ግጥሞች በአንድ መድብል ‹‹የፌስቡክ ትሩፋት›› በሚል ጠርዠዋለሁ፡፡ ማንም ቢፈልግ እዚያው ባለበት ማንበብ፣ ወይም ዳውንሎድ ማድረግ ይችላል፡፡ አምና ሁለት ሺህ ሦሰትን በአርባ ሁለት በሚል በ2003 የጻፍኳቸውን ጦማሮች አንድላይ ቢጠረዙ መልካም ነው በሚል ማስቀመጤ ይታወሳል፡፡ አሁንም ዘንድሮ የሞነጫጨርኳቸውን እዚህ አስቀምጫለሁ፡፡

በስህተቴ ያረማችሁኝን እና የነቀፋችሁኝን፣ በብርታቴ ላይ አበርታች የሆነ አስተያየታችሁን ለሰጣችሁኝ፣ በዝምታ ስታነቡኝ ከርማችሁ መንገድ ላይ ስታገኙኝ ለነገራችሁኝ እና ለሌሎቻችሁም ሁሉ ምስጋናዬ እንዲደርሳችሁ ከጉልበቴ ሸብረክ ማለቴን እንደምታስቡልኝ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡

አዲሱ ዓመት ሕልማችን የሚሞላበት፣ ለፍቅራችን ዋጋ የምንሰጥበት ይሁን፤ አሜን!

በ2004 የተጻፉ
  1. መንግስት ያልቻለውን እኛ ብንሞክረውስ?
  2. ሞክሮ መሳሳት እና ከስህተት መማር
  3. ፍቅር፤ ከፍቅር እስከ መቃብር (ልቦለድ)
  4. የአፋልጉኝ ማስታወቂያ ለተቃዋሚዎች
  5. የትራንስፎርሜሽኑ ዕቅድና አንዳንድ አካላት
  6. ኢትዮጵያውያን ለምን ዲቪ አይሞሉ?
  7. ደረሰኝ ሳይቀበሉ፥ ሒሳብ አይክፈሉ
  8. አሰብ የማን ናት?” በጨረፍታ
  9. ይህ - የታገልንለትን ጉዳይ አለማወቅ ነው
  10. አዎንታዊ ሀቆች ስለሊቢያ እና ጋዳፊ (Positive facts about Libya and Gadaffi) (ፌስቡክ ላይ ብቻ)
  11. ኢትዮጵያ ከኢሕአዴግ በኋላ፤ ሰጥቶ የመንጠቅ ዘመነ መንግስት
  12. In T1me - ጊዜ ገንዘብ (ገንዘብ ጊዜ) ቢሆን ኖሮ!
  13. “Every nation deserves its government” - ኦቶ ቮን ቢስማርክ
  14. የኢሕአዴግ ‹‹ትርፍ›› እና ኪሳራ
  15. ኢትዮጵያውያን፣ ኢትዮጵያ እያለች ሃገር የላቸውም
  16. የዳዊት ከበደ እና የተመስገን ደሳለኝ ወጎች
  17. ጨርቆስና ቦሌ - ሕይወትን እኛ እንደኖርነው!
  18. እስኪ ስለዋጋ - ቆም ብለን እናውጋ!
  19. ገመና 2 ሰው ለሰው፣ ጀግንነትና ኢትዮጵያ
  20. ሰማንያ ሚሊዮን እስከምንደርስ እንታገላለን
  21. የፈረንጅ አምልኮ በኢትዮጵያ
  22. የኢትዮ ቴሌኮም ቁልቁለት
  23. አፍንጫ ሲመታ ዓይን አያለቅስም ወይ?
  24. የሐበሻ አምልኮ በኢትዮጵያ
  25. አማርኛ በመዝገብ ላይ
  26. የቫለንታይን ጉርሻ ለወንዶች፤ የአዲስ አበባ ሴቶችን እንደታዘብኳቸው - ልማላችሁ! (ፌስቡክ ላይ ብቻ)
  27. ኑሮ በአገርኛ÷ ጾም ይበዛበታል!
  28. የአሜሪካ ኮንግረስ እና ሌሎችም ከኢትዮጵያ ፓርላማ መማር የሚገባቸው!
  29. ሦስት ሰዓታትን በግዞት (ፌስቡክ ላይ ብቻ)
  30. እቴጌ ጣይቱ ብጡል እና እቴጌ አዜብ መስፍን
  31. እንደ እርሳቸው ያለ ፊትም አልነበረ፤ አሁንም የለ፤ ምናልባት፣ ምናልባት ወደፊት ሊኖር ይችላል!
  32. ሕዝቦች ግለሰብን ይጨቁናሉ!
  33. እውትምሰሚ ያጡ ድምፆች!’
  34. መራመድና ባሉበት መሽከርከር፤ ሁለት የኑሮ ፈሊጦች
  35. እስኪ እንጠያየቅ፤ አገራችን የት ነው? (መጠባበቂያ ካስፈለገ)
  36. የቴዲ አፍሮን አልበም ያልገዛሁባቸው 5 ምክንያቶች
  37. ደጉ ኢትዮጵያዊ፤ ከልብ ካለቀሱ እምባ እንደማይገድ ያስመሰከረ ስብስብ
  38. የኢትዮጵያ መንግስት መጠላቱን የሚያሳብቁ ምልክቶች
  39. ከአከሌን አሰሩት እስከ አከሌን አገዱት!
  40. አብዮት ወረት ነው!
  41. የጋንዲ፣ ኪንግ እና ማንዴላ መንፈስ
  42. ዴሞክራሲ ኢትዮጵያ ውስጥ አለ ወይስ የለም? (እርስዎ ምን ይላሉ?)
  43. የመፈረጅ ፍራቻ እና የመፈረጅ አደጋ
  44. 21 ዓመት በኋላ (ዴሞክራሲ ሲሰላ)
  45. አሸባሪፊልምም ይታገድ ጀመር (በነገራችን ላይ ከወራት በኋላ ድጋሚ ለአንድ ሳምንት እንዲታይ ተደርጓል)
  46. የአንድ ኪራይ ሰብሳቢ መንግስት ታሪክ
  47. እነአልበርት አይንስታይን ስለዘንድሮው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምን ይላሉ?
  48. Hookah እና አሜሪካ
  49. የተመቻቸ ጊዜ መጠበቅ?
  50. አምስት የኢትዮጵያ ጠላቶች
  51. የባለፀጋዋን አገር ዜጋ፤ አቶ ድህነትን እናስተዋውቅዎ
  52. እውነቱ እና ፍርሃቱ
  53. የእንቆቅልሹ እንቆቅልሾች
  54. ጫወታ ስለየኦሎምፒክ ጫወታዎች
  55. ፋጡማ ኖረች አልኖረች፣ ጳጳሱ ኖሩ አልኖሩ…?
  56. የመለስ ሁለት መልክ
  57. ነውርን ማን ፈጠረው?
  58. በቁማቸው ከገደሉት በሞታቸው የገደሉት
  59. ኢሕአዴግ ቀይ እስክሪብቶ እኔ እንደወደድኩት (ዞን ዘጠኝ ላይ)
  60. ፎንቱ ፎኒፍ ሪፈታ ጄናን ኢቲሌን ጂቢቻ ካቴ(ዞን ዘጠኝ ላይ)
  61. የመለስ ዜናዊሀሁበስልጣን ጎዳና (ዞን ዘጠኝ ላይ)
  62. እውነት እና እስር ቤት (እስካሁን ለሰው ያላሳየሁት/ልቦለድ)

Saturday, September 1, 2012

በቁማቸው ከገደሉት በሞታቸው የገደሉት

From አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ


የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ሞት በብዙዎች ጉንጭ ለሁለት ወር ሲጉላላ ቆይቶ በኢትዮጵያ መንግስት ከተረጋገጠ ይኸው ሁለት ሳምንት ሊሆነው ጥቂት ቀናት ቀሩት፡፡ መንግስት ብሔራዊ የሐዘን ቀናት እስከዕለተ ቀብራቸው በማወጁ ባንዲራም ዝቅ ብሎ እየተውለበለበ ነው፣ መገናኛ ብዙሐንም ሙሉ ትኩረታቸውን በዚያው በሐዘኑ ጉዳይ ላይ እንዳደረጉ ናቸው፡፡ (በነገራችን ላይ የጡረተኛ ሚኒስትሮችን ጥቅማጥቅም የሚዘረዝረው የ2001 አዋጅ ላይ [አንቀጽ 11/1/ለ] ብሔራዊ የሐዘን ቀን አንድ ቀን እንደሆነ ይደነገጋል፡፡)

ኢትዮጵያውያን ወትሮም ቢሆን ሐዘን የማክረር ባሕላችን የተጋነነ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ሠልስት ሳይቀር እየተሰረዘ የሦስቱ ቀን ሐዘን ወደሁለት ዝቅ እንዲል ተደርጓል፡፡ በነገራችን ላይ የሐዘን ቀናት ወደሦስት ቀናት ዝቅ እንዲሉ የተደረገው በአፄ ምኒልክ አዋጅ የዛሬ መቶ ዓመት ገደማ ነበር፡፡ እንግዲህ በሰሞኑ፣ ሁለት ሳምንታት የዘለቀ የሐዘን ግዜ መቶ ዓመት ያህል ወደኋላ ተመልሰናል ማለት ይቻላል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር የሞተበት አገር ሕዝብ ማዘኑ አስገራሚ ላይሆን ይችላል፤ ነገር ግን በውዴታም ይሁን በግዴታ ይህንን ያህል ቀናት ማዘኑ ወይም እንዲያዝን ማድረጉ ብዙ ጥያቄዎችን ያጭራል፡፡ በዚህ ጽሑፍ የምናውራውም ከዚህ ፈር ከለቀቀ የሐዘን ግዜ በስተጀርባ ስላሉ ጉዳዮች ነው፡፡

አንድ፤ ችግር ይኖር ይሆን?

አገሪቱ አሁን እየተመራች ያለችው በተጠባባቂ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ነው ቢባልም፣ ያንን የሚያስመሰክር ነገር አላየንም፡፡ የመንግስት ልሳን የሆኑት እነ አዲስ ዘመን ሳይቀሩ ‹‹ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር›› እያሉ ነው የሚጠሯቸው፡፡ ከዚያም በላይ አሳሳቢው ግን በቶሎ የጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ማዕረግ በፓርላማ ምርጫ እንዲቀበሉ አለመደረጉ አጠያያቂ ነው፡፡ ምንም እንኳን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሞት በታወቀ በሦስተኛው ቀን ተመርጠው፣ ቃለመሓላ እንደሚፈጽሙ ቃል ተገብቶልን የነበረ ቢሆንም፣ መጀመሪያ ‹‹በአቡነ ጳውሎስ ቀብር›› በኋላም ደግሞ ‹‹የፓርላማ አባላት ሐዘናቸውን ይወጡ›› በሚሉ የማያሳምኑ ምክንያቶች ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል፡፡ ይሄ ቁርጥ ያለ ቀን ለማስቀመጥ ያለመወሰን ጉዳይ አሁንም በአቶ ኃይለማርያም ተተኪነት ላይ በግንባሩ ውስጥ (ከምስጢር ወዳድነቱ አንፃር) ስምምነቶች አለመኖራቸውን የሚያጠራጥር ነው፡፡